ሉቻኖ ቫሳሎ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ታሪክ የነበረው ለረጅም ዓመታት የሀገሩን ሰንደቅ ከፍ ያረገ አይረሴ ተጫዋች ነው ።
ፌዴሬሽናችን በ2008 ስውዲን ስቶኮልም አዘጋጅቶት በነበረው የ6ኛው ESCFE ላይ ከሌላኛው ባለታሪክ መንግስቱ ወርቁ ጋር የክብር እንግዳ እንደነበር እና ፌዴሬሽናችንም በሚገባው ልክ ባይሆንም ትልቅ አክብሮቱን ገልፆለት እንደነበር የሚታወስ ነው ።

ESCFE ባለፈው ዓመት በድንገት ያጣነውን ይህን ታላቅ ሰው ለመዘከር የአንደኛ ዲቪዚዮን ዋንጫውን “የሉቻኖ ዋንጫ” ሲል መሰየሙን ከትልቅ ክብር ጋር ይገልፃል ።